Tuesday, January 1, 2019

ጠላት ቁጥር አንድ- ስልክ

በልጆች እና በወላጆች መካክል፣ በልጆች እና በጤናማ አስተዳደግ መካከል፣ በልጆች እና በማህበራዊ ህይወት መካከል ጣልቃ የገባው  ጠላት ስልክ ነው።
አካላዊ ቅጣት የሚታይ እና የሚዳሰስ ቢሆንም በሞባይል ስልክ እና በመሰሎቹ የሚደርሰው ጉዳት በወቅቱ የማይታይ እና የማይዳሰስ የአአምሮ እና የአካላዊ ጤና ጉዳት ነው።
ስልክ ልጆችን ያለምንም ገመድ አስሮ የሚያቀምጥ ነገር ነው። ብዙ ወላጆችም ልጆቻቸው ሲሯሯጡ እና ሲረብሹ ስልክ በመስጠት ያስቀምጧቸዋል።

ማወቅ ያለብን፦ስልክም ሆነ ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ቴሌቪዝንን ጨምሮ ለልጆች አካላዊ እና ማህበራዊ ጤና ጠንቅ መሆናቸውን ነው።
ማውቅን ያለብን፦  በተለይ ከሶስት አመት በታች ላሉ ሕጻናት ስልክ በመስጠት ከሚገኘው ጥቅም ይልቅ ጉዳቱ ይበልጣል።
ማወቅ ያለብን፦ መቼ እና እንዴት መስጠት እንደሚገባ ነው።
ማወቅ ያለብን፦ ስልክም ሆነ ቴሌቪዝን ልጆችን ከወላጆች፣ ክማህበረሰቡ ይልቁንም ከራስቸው እንድሚያራርቃቸው ነው።
ማውቅ ያለብን፦ ስልክም ሆነ ቴሌቪዝን በአግባቡ ከተጠቀመንበት ጠቃሚ መሆኑን ነው።
ስልክ ለልጆች መቼ መሰጠት አለበት?
  1. ሆስፒታል- ለክትባትም ሆነ ለህክምና ልጆች ሲሄዱ በስልክ እንዲጫወቱ ማድረግ ለወላጅም ለልጅም እረፍት የሚስጥ ነገር ነው። ሆስፒታል ውስጥ ሲሯሯጡ ከሚመጣው ጭንቀት እና ረብሻ ይታደጋቸዋል።
  2. ለጉብኝት ወይም ዘመድ ጥየቃ ፦ በዚህ ጊዜ በተለይ ልጆች የሌሉበት እና ለእነሱ የሚሆን ነገር በሌለበት ቦታ ስልክ መስጠት ለወላጆችሁም ለልጆችም ጥቅም አለው። ወላጆች ጉዳያቸውን በእርጋታ ይጨርሳሉ። ልጆችም ሳይሰላቹ እና ሳይበሳጩ ይቆያሉ።
  3. ረዥም ጉዞ ሲያደርጉ፣
  4. እናት ወይም አባት የቤት ስራ በሚሰሩበት ጊዜ በተለይ ደግሞ ምግብ በሚያበስሉበት እና በሚያፀዱበት ጊዜ።
  5. በሰንበት ቀናት፣ በበአኣላት ወይም ልጆች ጥሩ ነገር ሲሰሩ እንድ ሽልማት።
ማውቅ ያለብን፦ ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ በተለይ ስልክ በቀን ከሁለት ሰአት በላይ እንዲጠቀሙ ማድረግ አደጋ አለው። አአምሯዊ ቅጣት ይሆናል

No comments:

Post a Comment